• "ተግዳሮት ፊታችን ሲጋረጥ፣ መልካም ዕድልንም ይዞ እንደሚመጣ ማመን፤ ተስፋ አለመቁረጥና ራስን ለአዲስ ነገር ክፍት ማድረግ ያስፈልጋል" በኩረ ትጉኅን ኃይለልዑል ገብረሥላሴ
    Feb 12 2026
    በኩረ ትጉኅን ኃይለልዑል ገብረሥላሴ፤ ከውልደትና ዕድገት፣ የትምህርትና ሥራ፣ የተግዳሮትና ስኬት የሠፈራ ሕይወታቸውን የዳሰሱበትን የግለ ሕይወት ትረካ በምልሰታዊ ምልከታ ይቋጫሉ። የወደፊት ትልማቸውንም ያጋራሉ።
    Show More Show Less
    13 mins
  • በኩረ ትጉኅን ኃይለልዑል ገብረሥላሴ፤ ትምህርት፣ ሥራና የአውስትራሊያ ክብር ሽልማት
    Feb 12 2026
    በኩረ ትጉኅን ኃይለልዑል ገብረሥላሴ፤ በሀገረ አውስትራሊያ ከመንፈሳዊ የአገልግሎት ተልዕኳቸው ጎን ለጎን ስላካሔዷቸው የትምህርትና የሥራ ዓለም ሕይወታቸው ነቅሰው ያወጋሉ።
    Show More Show Less
    22 mins
  • በኩረ ትጉኅን ኃይለልዑል ገብረሥላሴ፤ ከነገሌ ቦረና እስከ አውስትራሊያ
    Feb 10 2026
    በኩረ ትጉኅን ኃይለልዑል ገብረሥላሴ፤ ከውልደት ቀዬአቸው ነገሌ ቦረና እስከ ሁለተኛ ሀገራቸው አውስትራሊያ የተጓዙበትን የመንፈሳዊና ዓለማዊ ግለ ሕይወት ታሪካቸውን ያጋራሉ።
    Show More Show Less
    21 mins
  • ሀገራዊ ቃል ኪዳን "ባለቤቴን ለትዳር ስጠይቃት 'እኔ ሀገሬ ላይ ነው መኖር የምፈልገው፤የአንቺ ሃሳብ ምንድነው? ይህን ማወቅ አለብኝ አልኳት' ዳንኤል አለማር
    Aug 30 2025
    ዳንኤል አለማር፤ በቀዳሚው ክፍለ ዝግጅታችን የግለ ታሪክ ወጉ እንደምን በለጋ የወጣትነት ዘመኑ ከእነ ቤተሰቡ ለሀገረ ኬንያ የስደት ሕይወት እንደበቃና እንደተወጣው አውግቷል። በመቋጫው፤ የአውስትራሊ አዲስ የሕይወት ምዕራፍ ጅማሮውን፣ ተግዳሮቶችና መልካም ዕድሎችን አንስቶ ይናገራል።
    Show More Show Less
    23 mins
  • "ለዛሬ መድረሻዬ ሆነኝ የምለው፤ በስደት ካምፕ የነበረኝና የሰንቅኩት ሕይወት ነው" ዳንኤል አለማር
    Aug 30 2025
    "የኃይለ ሥላሴ ቤተሰብ ነው እንዳትነኩት" - ዳንኤል አለማር፤ በግለ ታሪክ ወጉ ገና ለአካለ መጠን ሳይደርስ በለጋ ዕድሜው ከእናትና ወንድሞቹ ጋር እንደምን የትውልድ ሀገሩን ኢትዮጵያን ለቅቆ ለኬንያ የስደት ካምፕ እንደተዳረገና የኢትዮጵያ ስም እንደምን ከእሥር እንዳስለቀቀው ነቅሶ ያወጋል።
    Show More Show Less
    13 mins
  • "ኢትዮጵያውያን መጥተው ድጋፋቸውን ቢቸሩኝ ደስ ይለኛል" ሶሊያና እርሴ
    Apr 3 2025
    አንፀባራቂ ኮከብ በመሆን ላይ ያለችው ሶሊያና እርሴ፤ ከትውልድ ከተማዋ ጎንደር፣ ከዕድገት ክፍለ ሀገሯ ትግራይ ተነስታ፤ እንደምን ትንፋሽን የሚያስውጥ፣ የልብ ትርታን ከፍና ዝቅ የሚያደርግ፣ ምትሃታዊ እንጂ ከቶውንም የመድረክ ዕውነታ የማይመስለው፤ ግና ሞገስን የተላበሰ አካላዊ መተጣጠፍ ኮንቶርሽን ተጠባቢ ለመሆን እንደበቃች ታወጋለች። ከኤፕሪል 3 እስከ ሜይ 11 በሜልበርን ከተማ Meat Market ከ Club Kabarett ጋር በመሆን ለሕዝብ ስለምታቀርበው ዝግጅቷ ታነሳለች። የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላትም በሥፍራው እንዲገኙ ትጋብዛለች።
    Show More Show Less
    9 mins
  • "የትም ሀገር ብንሆን ኢትዮጵያን ከውስጣችን ማውጣት አይቻልም፤በአፍሪካ የመጀመሪያው በሆነው የሰርከስ ማዕከል ግንባታ ኢትዮጵያውያን ተሳታፊ ቢሆኑ ደስ ይለኛል"ሶስና ወጋየሁ
    Jan 29 2025
    የቀድሞዋ ኢትዮ - ሰርከስ ኮከብ አባልና የኢትዮ - ሰርከስ ኢንተርቴይንመንት ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሶስና ወጋየሁ፤ ከግለ ሕይወት ታሪካቸው ጋር አሰናስለው እንደምን ከሀገረ አውስትራሊያ ወደ ሀገር ቤት በመመለስ፤ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሚሆነውን የሰርከስ ማዕከል በእንጦጦ ፓርክ በመገንባት ላይ እንዳሉ ይናገራሉ።
    Show More Show Less
    22 mins
  • ሶስና ወጋየሁ፤ ከአውስትራሊያ ጥገኝነት ጥየቃ ለክብር ሽልማት መብቃት
    Jan 21 2025
    የቀድሞዋ ኢትዮ - ሰርከስ ኮከብ አባልና የኢትዮ - ሰርከስ ኢንተርቴይንመንት ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሶስና ወጋየሁ፤ እንደምን በሀገረ አውስትራሊያ ከጥገኝነት ጥየቃ ለከፍተኛ የክብር ሽልማት እንደበቁ ያወጋሉ።
    Show More Show Less
    14 mins